Showing all 5 results
-
-
-
የመደመር መንገድ
$20Add to cartሀገር የሚመራበት ሥርዓት ሚዛኑን ጠብቆ እንዲጓዝ የሚያስችሉት ብዙ ነገሮች ይኖራሉ፤ ዋነኞቹ ግን ተቋማት ናቸው። እነዚህ ተቋማት ዐቅማቸው እየደከመ ሲሄድ በሥርዓቱ ውስጥ ግለሰቦች ጉልበታቸው እንዲፈረጥም ዕድል መፍጠሩ አይቀርም። ለምሳሌ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ዲሞክራሲ ሊወለድባቸው ገና ብዙ ትግል በሚቀራቸው ሀገራት ነጻ የፖሊቲካ እንቅስቃሴ ለማካሄድ ሜዳውን ለሁሉም ክፍት ማድረግ ብቻ አይበቃም። ሂደቱ ያለ ችግር እንዲከናወን፣ ግለሰቦች ያለመሸማቀቅና ያለጥቃት እንዲሳተፉ፣ የዲሞክራሲና የፍትሕ አካላት ሚዛን የመጠበቅ ሚናቸውን በአግባቡ መወጣት ይኖርባቸዋል። ይህ ካልሆነ የሥርዓቱ ሚዛን የሚጠበቀው በግለሰቦች በጎ ፈቃድ መልካም ስብእና ላይ ተመስርቶ ይሆናል።
-
የታፋኙ ማስታወሻ
$18Add to cartከጥቂት ሰአታት በረራ በኋላ ከዱባይ የተነሳው አውሮኘላን ሰነአ አሰም አቀፍ አየር ማረፊያ ደረሰ። ሁሉም ተሳፋሪ ወረደ፡፡ ጥቂቱ ተሳፋሪ አዛው ሰነአ ቀሪ ነው፡:……. አኔም አንደሌሎች ተሳፋሪዎች በዚህ አውቶቡስ ላይ ተጫንኩ-: አውቶቡሱ ብዙ ርቀት አልፄደም። ከአንድ ህንጻ ፊት ቆመ: ተሳፋሪዎችን ተከትዬ እኔም ከአውቶቡሱ ወረድኩ: አነሉን ተከትዬ ወደ ህንጻው ተጓዝኩ: ለመጀመሪያ ጊዜ ክዚህ ጉዞ ጋር የተያያዘው ስጋቴ እውን ሊሆን እንደሚችል ፍንጭ አየሁ።
-
የከተማው መናኝ ኤልያስ መልካ
$19Add to cart“ተገርሜ አግብቶ ነበር እንዴ? ብዬ ጠየኩት። ቀለበት አስሮ ነበር ብሎ መለሰልኝ። ቀለበት ቀለበት? ስለው ሳቀ። ጣቱን እያመለከተ እኔ እንዳደረኩ ዓይነት ቀለበት አድርጎ ነበር መሰለኝ አለኝ። ማን ጋር ይሆን? ብዬ ለአፍታም አልተጠራጠርኩም። የፍቅር ምርጫየ የሙዝቃ ቪድዮ የተሰራው ነሀሴ 1996 ዓ.ም ነው። በዚህ ወቅት አብራው የነበረችው ሴት ደግሞ ዮዲት ናት።”
”ኤልያስ እንቅልፍ ውስዶታል። ፊትም ሙሉ በሙሉ ተቀያይሯል። በጤንነቱ ጊዜ የነበረው መልኩ ተመልሷል… ደነገጥኩ። በስመ አብ ወ ወልድ ብየ አማተብኩ። ኤልያስ! ኤልያስ… እያልኩ ተጣራሁ። ብንን ብሎ ፊቱን እየጠራረገ ቆንጆ ሕልም እያየሁ ነበር አቋረጥሽን አለኝ። ምን? አየህ ብየ ጠየኩት።
በአራንጓዴ ሜዳ ላይ አንዲት ቀጭን መንገድ አገኘሁ በእሷ የሆነ በጣም የሚያምር ቦታ ደርሼ መጣሁ…”
